
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በኢንጂነሪንግ ፣ በጤና እና በቢዝነስና ማህበራዊ ጥናት ኮሌጆች በ2018 የትምህርት ዘመን በተለያዩ ከ 30 በሚልቁ የመጀመሪያ ዲግሪ እና የሁለተኛ (ማስተርስ) ዲግሪ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ በመደበኛ መርሃ-ግብር በክፍያ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቋል።
ስለሆነም አመልካቾች ከሰኞ ነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 29/2017ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዋና መስሪያ ቤት ፣ ሬጅስትራርና ምሩቃን ጉዳይ ፅ/ቤት ዘወትር በስራ ቀናት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።